Shir-Shir Ethiopia

Shir-Shir Ethiopia We work for people in the journey and Shir-shir Ethiopia is the open gate to rediscover the new face of Ethiopia

11/10/2025
new year colours ,spring flowers, 🌺 clean rivers and good time for trekking, Addis River restoration, healing the self a...
05/10/2025

new year colours ,spring flowers, 🌺 clean rivers and good time for trekking, Addis River restoration, healing the self and connect to nature conscious guidance.

26/08/2025

አደን በጣም ይወድ የነበረ ንጉሥ ከአንድ አብሮ አደግ ጓደኛው ጋር ወደ ጫካ ወጣ እያሉ ብዙ ቀን ያድኑ ነበር፡፡ የንጉሡ ጓደኛ አንድ ገጠመኝ ሲገጥመው “ለበጎ ነው" የማለት ልምድ ነበረው።

አንድ ቀን ሁለቱ አደን እያደኑ ጓደኛው ጠመንጃውን እያቀባበለ ለንጉሡ ይስጣል፤ ንጉሡ ይተኩሳል፡፡ አንዴ ግን ጓደኛው ጠመንጃውን ሲያቀባብል ስህተት ስለሠራ ንጉሡ ሲተኩስ አንድ ጣቱ ተቆረጠ፡፡ ንጉሡ በሁኔታው ሲበሳጭ ጓደኛው ግን እንደተለመደው “ለበጐ ነው" አለ፡፡ ንጉሡም “ይኸማ ለበጐ አይደለም!" በማለት በንዴት ጮኽ፡፡ ወዲያውኑ ጓደኛውን እስርቤት አስገባው፡፡

ከአንድ ዓመት በኋላ እንደተለመደው ንጉሡ ራቅ ያለ ጫካ ለብቻው ሄዶ እያደነ ነበር፡፡ ነገር ግን በአካባቢው ከሌላ ቦታ የመጣን ሰው ሲያገኙ ገድለው በማቃጠል ለአምላካቸው መሰዋዕት የሚያቀርቡ ሰዎች እንዳሉ ንጉሡ አያውቅም ነበር፡፡ ስለዚህ ሳያስበው በድንገት ከበው በመያዝ እጁን ወደኋላ አስረው ወደሚገደልበት እና የሚቃጠልበት ቦታ ወስዱት፡፡ ነገር ግን ሊገድሉት ሲሉ ንጉሡ አንድ ጣት እንደሌለው አዩ፡፡ በእምነታቸው መስረት ሙሉ አካል የሌለው ሰው ለመስዋዕትነት አይሆንም።

ነበር፡፡ ስለዚህ በተቆረጠችው ጣቱ ምክናያት ንጉሡ ሕይወቱ ተርፎ ወደቤቱ ተመለሰ፡፡

እየተመለሰ እያለ ጣቱ የተቆረጠበትን ቀን በማስታወስ “እውነትም ለበጐ ነበር" በማለት ጓደኛውን ማሰሩ በጣም ፀፀተው፡፡ እንደደረሰም ቀጥታ ወደ እስር ቤት በመሄድ “አሁን ሳየው ያኔ አንተ ልክ ነበርህ" አለ ለጓደኛው፡፡ “ጣቴ ያኔ መቆረጡ ለበጎ ነበር' በማለት ያጋጠመውን በዝርዝር ነገረው፡፡ “ስለዚህ አንተን ማሰሬ ስህተት ነበር፡፡ በጣም ይቅርታ'' አለ ንጉሡ፡፡

ጓደኛውም “ተሳስተሀል፡፡ መታሰሬ ለበጐ ነበር' አለ፡፡ ንጉሡ ግራ በመጋባት “ምን ማለትህ ነው? እንዴት ጓደኛዬን እስር ቤት ማስገባቴ ለበጐ ይሆናል" አለ፡፡ ጓደኛውም “ይሄኔ እስርቤት ባልገባ ኖሮ እዚያ ቦታ ለአደን አብረን እንሄድ ነበር፡፡ ጣትህ መቆረጡን ሲያዩ አንተን ለቀው እኔን ይገድሉኝ ነበር" አለው፡፡

👉▪▪▪ሁሉም ነገር ለበጐ ነው▪▪▪

◉◉ ©️Days and Colours 2 tube

25/08/2025
Visit Gurage
25/08/2025

Visit Gurage

#አዳብና ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች ለመገናኘት ችግር በነበረበትና ቴክኖሎጂ ባልተስፋፋበት ዘመን አባቶቻችንና እናቶቻችን በትዳር በማገናኘት ሀገር ያስቀጠለ ባህል ነው።

#የአዳብና በዓል አከባበር በሶዶ ክስታኔ ማህበረሰብ ዘንድ ከመስቀል በዓል ቀጥሎ ከመስከረም 16 እስከ ጥቅምት 5 በገበያ ቦታዎች፣በኃይማኖታዊ ቦታዎች እና በበዓሉ ማክበሪያ ቦታዎች ላይ በልዩ ድምቀት የሚከበር በዓል ነው፡፡

#አዳብና ከመድረሱ በፊት ወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች በማህበረሰቡ ባህል መሰረት አዲስ ልብስ ጫማና ጌጣጌጣቸው ያዘጋጃሉ ሹሩባቸውም ይሰራሉ ወንዶቹም ፀጉራቸው ተቆርጠው አምረውና ደምቀው ሴቶቹም የወንዶችን አይን ውስጥ ለመግባት ወንዶቹም ልጃገረዷን ለማማለል ዝግጅታቸውን በሙሉ ያጠናቅቃሉ።

#አዳብና በዓል ባህላዊ የወጣት ወንዶችና የልጃገረዶች የአደባባይ በዓል ሲሆን የወጣት ወንዶች አባትና እናት ልጃቸው ሚስት ሊለመንለት ሲደርስና ሲታሰብ በጓደኛው በኩል በአዳብና ላይ የምትሆነው አጭቶ እንዲመጣ ከተነገረው በኃላ አዳብና ላይ አይቶ አይኑ ያረፈባት በሎሚ መርጦ በመምታት ጥያቄው የተቀበለቺው ልጃገረድ እንድትለመንለት ይነግራል ብዙ የግንኙነት እድል ባልነበረበት ዘመን ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ ወጣቶችና ልጃገረዶች የሚተጫጩበት ውሃ አጣጭ የሚመርጡበት በዓል ነው።

#አዳብና ከወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች በተጨማሪ የዘመኑ ሙሽሮች ከጫጉላ ቤት(ከጎለት የወጡ) ወግአቸው የሚያዩበት ደምቀው የሚታዩበት በሴት እና በወንድ ሚዜዎቻቸው ተከበው ባገባችበት የባህል ልብስ ፀጉሯን ተሰርታ ዣንጥላ ይዛ ትወጣለች አምራና ደምቃ ከታየች ጥሩ ቤት ገብታለች በጥሩ ሁኔታ እንደተሞሸረች አማቾቿ ቤት ምስጋናና አድናቆት ይነገርላቸዋል እሷም ሙሽራ እንደመሆኗ መጠን እያፈረች እና እየፈራች ላለመታየት በዣንጥላዋ ተከልላ ትውላለች ጓደኞቿም ማስቲካና ከረሜላ እየሰጡ ያጫውቷታል ፕሮግራሙ ሲያልቅ በጊዜ ሳይመሽ የአንድ አካባቢ ልጆች ተቃቅፈው እና ተሰባስበው እየተጫወቱ እየጨፈሩ ወደ አካባቢያቸው ይመለሳሉ።

#ሌላኛው የአዳብና በዓል ተጨማሪ ውበት ገፅታ የሚሰጠው ከአበባው ጋር የሚነሳባቸው የሙየቶች እንቅስቃሴ፣ዜማ፣ጫወታና ጭፈራ ልዩ ትይንት የበለጠ ጫወታው ያደምቁታል።

#አዳብና የተለያዩ የጨዋታ አይነቶች አሉት ከእነዚህም ውስጥ ወንዶች እና ልጃገረዶች አብረው ክብ ሰርተው ወንዶች በጉረሮ ማንጎሮ ዜማና ግጥሞች በሚያወጡት ልዩ ድምፅ እና በጭብጨባ ልጃገረዶቹ በከበሮና በጭብጨባ የተወሰኑት ወንዶችና ልጃገረዶች ደግሞ በክቡ መሐል በመግባትና በመጨፈር የሚያሳዩት ትርኢት አንዱና ዋነኛው ሲሆን የበትር ዝላለ፣ነጆ አራጆ፣ሰባ፣አጋቲ፣የበትር ዝላለ፣ እና የፈረስ ጉግስ ጫወታዎችም የሚጫወቱበት ነው።

#ወጣት ወንዶች ለቡሄና ለመስቀል ሆያሆዬ በመጨፈር ያገኟትን ነገር አጠራቅመው አዳብና ጨዋታ ላይ ልባቸው ለከጀላት ኮረዳ እና እርስ በእርሳቸው (ሳኩሜ፣መሪ፣ሞጎ) ጋር (ሎሚ፣ ማስቲካ፣ከረሜላ፣ብርትኳንና ጥንቅሽ) ገዝተው ይሰጣጣሉ አብረው ይበላሉ።

#ልጃገረዶችም በበኩላቸው በዐዲስ ዓመት (አክራሚ ቀን) "አዬ አዬ" እያሉ እንጊጫ በመንቀልና ለአዲስ ዓመት እንቁጣጣሽ በመጨፈር ለአዳብናቸው ገንዘብ ያጠራቅማሉ በተመሳሳይ ከጓደኞቿ(አዶዬ፣የጎስቴ፣የብጤና አዶዬ) ጋር ስጦታ ይሰጣጣሉ አብረው ይበላሉ።

#በአጠቃላይ የአዳብና በዓል ተሳታፊ ወጣቶች የቀድሞ ይዘቱ ይዞ እንዲከበር የጠበቁ አለባበስ ፣ የፀጉር አሰራር አቆራረጥ አጋጌጦች ባህላዊ ጨዋታዎች እንዲከበርና ሚዲያዎችና ግለሰቦች ይህንኑ ማስተዋወቅና በዓሉ ድሮ ወደ ነበረበት የመመለስ ሂደት መደገፍና እስከ ማምሻ ድረስ ባለመቆየት ለጎጂ ልማዳዊ ድርጊቶች ተጋላጭ እንዳይሆን ከቀኑ 11:00 ሰዓት ድረስ መጠናቀቅ እንዳለበት ተቀናጅቶ መስራት ያስፈልጋል።

#አዳብና ከባህላዊ እሴትነቱ ባሻገር ማህበራዊ ፋይዳው የላቀና ሁሉ አካል ሳይለይ እና በአካባቢ ሳይታጠር ሁሉንም በእኩልነት የሚታደምበት የሁላችንም በዓል በመሆኑ ተቋማትና ተወላጁ በብሔራዊ የማይዳሰስ ቅርስነት ከማስመዝገብ አልፎ በዩኔስኮ ለማስመዝገብ ሰፊ ስራዎች መስራት ያስፈልገናል።

Via ተሻለ ነገሰ page

Visit Gurage
Visit Ethiopia

"እነሆ ንጉሳችን "አዲስ ዓመት ባከበርን ቁጥር ልናስታውሰው የሚገባን ቅኝ ገዢዎች ያልቀየሩት የዘመን አቆጣጠር  ታሪክ ነው::ታላቁን ቁማር የበላችው የምስራቋ ኮኮብ ሀገራችን ኢትዮጵያ  በነገ...
25/08/2025

"እነሆ ንጉሳችን "
አዲስ ዓመት ባከበርን ቁጥር ልናስታውሰው የሚገባን ቅኝ ገዢዎች ያልቀየሩት የዘመን አቆጣጠር ታሪክ ነው::

ታላቁን ቁማር የበላችው የምስራቋ ኮኮብ ሀገራችን ኢትዮጵያ በነገስታቶቿ እና በሕዝቧ ብርታት ነበር::

ከ 15ኛው ከዘመን በፊት የታቀደው ታላቁ ቁማር:

1ኛ. መጀመሪያ መንግስታቸውን እናጥፋው ወይም እናዳክመው, ስልጣኔአቸውን ታሪካቸውን, ፊደላቸውን, የቀን መቁጠሪያቸውን, እናጥፋው

2.ለእኛ አላማ የሚመች ሌላ ታሪክ እንፃፍላቸው,/ ድሀ, የድሀ ድሀ, ጨለማው አህጉር ሁዋላ ቀር.. መሀይም.. ውዘተ/ ማን እንደሆኑ እኛ ስም እናውጣላቸው

3ኛ. መንግስታቸውን ካጠፋን በሁዋላ የባሪያ ንግድ በመጀመር ያለ ምንም ከልካይ የሰው ሀይል እንውሰድ.. ሀገራችንን እንገንባ
( 18 ሚሊዮን ወጣት አፍሪካውያን ተወሰዱ )
4ኛ. መንግስት ስለሌላቸው ተመልሰን ሄደን እኛ እናስተደዳራችሁ እናሰልጥናችሁ እንበላቸው :: መንግስታችንን ሀገራቸው ላይ እንመስርት..የኛን ባህል የኛን ቋንቋ እናስተምራቸው... ቅኝ እንግዛቸው

5ኛ. በጎሳ, በሀይማኖት, እንከፋፍላቸው...

ለምሳሌ ሩዋንዳን ቤልጄም ነች ቅኝ የገዛችው.. ያኔ ለዜጎች የተሰጠ መታወቂያ ሁቲ እና ቱሲ የሚል ነበር:: ከብዙ ዓመት በሁዋላ ለሚሊዎኖች እልቂት ምክንያት ሆነ::

6ኛ. ድሆች መሆናቸውን ከነገርናቸው በሁዋላ እንርዳችሁ ብለን ተመለሰን እንሂድ:: ዕድገታቸውን እንቆጣጠር.. እንዳይሰሩ የሚያደርግ እርዳታ እንስጣቸው.. ብድር እንስጣቸው..

7ኛ.. ሰላም እንዳይኖር እናድርግ.. እርስ በርሳቸው እንዲጣሉ እንስራ, ተረጋግተው እንዳይኖሩ እናድርግ::

ምንም ይሁን ምን ጠንካራ መንግስት እንዳይኖር እናድርግ::
ይሄ ነበር ቁማሩ::
ይሄን ቁማር ሁሉም ቦታ ላይ ሲሳካላቸው ኢትዮጵያ ላይ ብቻ አልሆነም::

ያኔ ኢትዮጵያ እንሆ ንጉሳችንን እየዘመረች ነበር::
ምክንያቱም አፍሪካ በሙሉ ንጉስ አልባ እና መንግስት አልባ አድርገውት ነበርና...

ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ
አይነካም ነፃነትሽ
ተባብረዋል አርበኞችሽ
ብርቱ ናቸው ተራሮችሽ
ድል አድራጊው ንጉሳችን
ይኑርልን ለክብራችን

ኢትዮጵያን ለመረዳት የአፍሪካን ታሪክ መረዳት ይጠቀማል::
አፍሪካን ለመረዳት ኢትዮጵያን መረዳት ይጠቀማል::

ኢትዮጵያ ቅኝ እንዳትገዛ የኢትዮጵያ "ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ነገስታቱን በማማከር በመፀለይ እና ሕዝቡን በማስተባበር ኢትዮጵያን ለድል አብቀተዋል::" / The politics of southern Africa / የተባለ መፅሐፍ ውስጥ በደቡብ አፍሪካ ፕርፌሰሮች የተፃፈ::
ከአድዋ ድል በሁዋላ በሰባት የተለያዩ አለማት ውስጥ በውጪ ዜጎች የአቢሲኒያ ቤ/ ክርስትያን የሚባሉ ቤ/እምነቶች ተቋቁመው እስካሁን ድረስ አሉ::

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክ የእምነት ተቋም ብቻ ሳትሆን ለጥቁሩ እና ጭቆናን ለሚቃወም ሁሉ የነፃነት ምልክት በመሆን በዓለም ታወቀች::
የኢትዮጵያ አዲስ አመት የዘመን አቆጣጠሩን ቅኝ ገዢዎች ስላልቀየሩት ከዓለም የተለየ የሆነው በዚህ ምክንያት ነው::

አፍሪካ ከቅኝ ግዛት በፊት የሚለዉን ታሪክ ሊንኩ እነሆ

https://youtu.be/We30uXDzq7s?si=PcH9yX88LqNt484t

አክባሪያችሁ
ፍሬአለም ሺባባው

In 1884, the fate of an entire continent was decided—without a single African voice in the room.This is the untold story of the Berlin Conference, where Euro...

24/08/2025


በዚህ ጊዜ በወንዶችና በሴቶች አደገኛ ፈተና የሆነው ዝሙት ነው። የሰው ልጅ ማለት ሴቷ ወንድ ልጅ የምትፈልግበት ወንዱም ሴት ልጅ የሚፈልግበት የተፈጥሮ ስጦታ አለው ። ቅዱስ ጳውሎስ" ነገር ግን ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን" ( 1ኛ ቆሮ 14:40) እንዳለው

ማንኛው ሰው ተፈጥራዊ ስሜት ይንሮው እንጂ እንደ እንስሳ ሳይሆን በስርዓት መሄድ ይኖርበታል አንድ ሰው በሂወቱ ሃላፊነት ካልወሰደ በስተቀር ማንም ሃላፊነት ሊወስድለት አይችልም።

ወንዱ ይሁን ሴቷ የእግዚአብሔር ሕግ ከማስቀደም ይልቅ ፋሽን እየተባለ ወንዱ በየቀኑ ሴቶችን እንደ ልብስ እየቀያየረ ፣ ሴቷም በየቀኑ ወንዶች እንደ ልብስ እየቀያየረች ወደ ሞት ይነዳሉ። ይህ የዝሙት መንፈስ የተጠናወተበት ሰው በስጋው ይሁን በነፍሱ የረከሰና የድያብሎስ መኖርያ ይሆናል። አላስተዋልም እንጂ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍስሶ በዋጋ የገዛን በመሆናችን በራሳችን ላይ ከእግዚአብሔር ሕግ ውጭ የማድረግ ስልጣን የለንም።
ሰለዚህ እኛ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ነን(1ቆሮ 3:16) ።

ታድያ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ናችሁ ከተባልን የእግዚአብሔር መንፈስ መኖርያ እንሆን ዘንድ ከዝሙት መራቅ አለብን አለበለዚያ ንስሐ ሳንገባ በዝሙት ተጠምደን የምንኖር ከሆንን ግን ነፍሳችን ከእግዚአብሔር ፀጋ ተራቁታ ወደ ሲኦል ትገባለች ዝሙት የነፍስና የስጋ በሽታ መሆኑን የአምላክ ቃል እንዲህ ብሎ ያስተምረናል፦

🚺🚹 " ማንም የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ ቢያፈርስ እግዚአብሔር እርሱን ያፈርሰዋል፤ የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ቅዱስ ነውና፥ ያውም እናንተ ናችሁ " ( 1ኛ ቆሮ 3:17) ።

✅ እስኪ ከመፅሓፍ ቅዱስ ስለ ዝሙት ምን እንደሚል አብረን እንመልከት፦

✅ " እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ያለ ዝሙት ምክንያት ሚስቱን የሚፈታ ሁሉ አመንዝራ ያደርጋታል፥ የተፈታችውንም የሚያገባ ሁሉ ያመነዝራል "( ማቴ 5፥32)።

✅ " ከልብ ክፉ አሳብ፥ መግደል፥ ምንዝርነት፥ ዝሙት፥ መስረቅ፥ በውሸት መመስከር፥ ስድብ ይወጣልና" ( ማቴ 15:19)።

✅ " ለጣዖት ከተሠዋ፥ ከደምም፥ ከታነቀም፥ ከዝሙትም ትርቁ ዘንድ ከዚህ ከሚያስፈልገው በቀር ሌላ ሸክም እንዳንጭንባችሁ እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናልና፤ ከዚህም ሁሉ ራሳችሁን ብትጠብቁ በመልካም ትኖራላችሁ።ጤና ይስጣችሁ " ( ሐዋ.ሥራ 15:28-29)።

✅ " በቀን እንደምንሆን በአገባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፥ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፥ በክርክርና በቅናት አይሁን ( ሮሜ 13:13)።

✅ " በአጭር ቃል በእናንተ መካከል ዝሙት እንዳለ ይወራል የዚያም ዓይነት
ዝሙት በአሕዛብስ እንኳ የማይገኝ ነው፥ የአባቱን ሚስት ያገባ ሰው ይኖራልና( 1ኛ ቆሮ 5:1)።
✅ " መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። ሥጋ ግን ለጌታ ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም፤ ጌታም ለሥጋ ነው " ( 1ኛ ቆሮ 6:13)።
✅ " ከዝሙት ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጭ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል" ( 1ኛ ቆሮ 6:18)።

✴✳ ታድያ ምን እናድርግ? ✳✴

✅ እስከሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ ( ራእ.ዮሐ 2:10)። ይህ የህይወት አክሊል የሚገኘው በፆም ፣ በጸሎት፣ በስግደት፣ ንስሐ ገብተን በቅዱስ ቁርባን መኖር፣ አስራት በኩራት በማውጣት ስንኖር ነው። ቅዱስ አምላካችን በማቴ 6:33። ላይ " ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል" እንዳለው

©מולוקו יזגאו

27/11/2024

Ethiopia’s musical queen, Ejigayehu ‘Gigi’ Shibabaw, has joined the legendary Gladiator 2 score, collaborating with global icons to create a masterpiece that will echo through history! 🌍🎶

Credit: Addis Insight

Address

Madagascar Street
Addis Ababa
251

Telephone

+251(0)920656690

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Shir-Shir Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Shir-Shir Ethiopia:

Share