07/10/2025
Today I had the honor of celebrating World Animal Day at Feven – Animals Need Attention Initiative, a shelter founded with such a compassionate heart for animals in need.
We celebrated together with dogs who once lived on the streets of Addis Ababa, but today found love, care, and dignity. I also had the chance to voluntarily vaccinate 20 dogs against rabies — a small step to keep them and our community safe. 🐶💉
I’m truly inspired by Feven’s kindness and dedication. She not only rescues and shelters dogs but also cares for a brave donkey who survived cruelty and even hyena attacks. 🐴❤️
Her work is a shining example of compassion in action. 🙏✨
Let’s all remember: every animal deserves care, protection, and respect. 💚
የአለም የእንስሳት ቀን በእንስሳት ትኩረት ይሻሉ የእንስሳት ማቆያ !!!
ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት ላይ በምትገኘው ሱሉልታ በእንስሳት ትኩረትን ይሻሉ መስራች ፌቨን መለሰ የተከፈተውን የእንሳት ማቆያ (shelter) በጥቂቱ ልንገራችሁ። በዚህ የእንስሳት ማቆያ በጎዳና ላይ የነበሩ እና በተለያየ የአካል ጉዳት ላይ ያሉ ወደ 25 የሚጠጉ ውሾች ሲኖሩ በተጨማሪም ባለቤቶቿ ተጠቅመው የጣሏት ከጅብ ንክሻ የተረፈች አንዲት አህያ አለች። በእውነቱ ከሆነ በዚህ ቦታ ላይ በመገኘቴ በጣም ደስ ብሎኛል ኮርቻለሁም። ይህንን ስራ መንግስት መስራት ያለበት ስራ ሆኖ ሳለ በአንዲት ጎበዝ ፣ ጠንካራ እና ሩህሩህ ልብ ያላት እንስት መከፈቱ የሚያስመሰግን እና ሊበረታታ የሚገባው ተግባር ነው።
መስከረም 24 የተከበረውን የአለም እንስሳት ቀን ምክንያት በማድረግ እኔ በበኩሌ የራሴን አሻራ ለማሳረፍ መጠለያው ውስጥ ያሉ ውሾትን የውሻ እብደት በሽታ በተሳካ ሁኔታ ከትቤያለሁ። ከዚህ በተሻለ ደግሞ እንደ አንድ ግለሰብ እና የእንስሳት ጤና ባለሙያ ይህንን የተቀደሰ ሃሳብ በተቻለ መጠን ለማገዝ ከፈጣሪ ጋር የቻልኩትን አደርጋለሁ።
እንዲህ ያለ መጠለያ (shelter) በእንስሳት ደህንነት ላይ ትልቅ ሚና አለው። ይህም እንስሳትን ከጎዳና ሕይወት ያወጣል፣ በበሽታ እና በተለያዩ አካላዊ ጥቃት የተጎዱትን ያድናል፣ የተመቻቸ ህክምና እና እንክብካቤ እንዲያገኙ ያደርጋል እንዲሁም በዋነኝነት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር እና በጎዳና ላይ ያሉ የእንስሳትን ቁጥር በመቀነስ ለሰው እና ለእንስሳት ደህንነት ይረዳል። 🏠💚
በእውነቱ ፌቨን ለጀመረችው ነገር ትልቅ አክብሮት አለኝ። የበለጠ አድጎ ትልልቅ ነገሮች እንደሚኖሩት ተስፋ አደርጋለሁ በርቺ ለማለትም እወዳለው። ይህን ፅሁፍ የምታነቡ ፌቨንን በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች "እንስሳት ትኩረትን ይሻሉ"( Animals Need Attention) ብላችሁ በመፈለግ ማግኘት ትችላላችሁ።
ይህንን እናስታውስ "ማንኛውም እንስሳ ፍቅር፣ እንክብካቤ እና ክብር ይገባዋል።"
በዶ/ር አልአዛር አየለ
#የአለምእንስሳትቀን
#እንስሳትትኩረትይሻሉ